የስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት

የስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ተግባርና ኃላፊነት

የስነ-ምግባር፣ መልካም አስተዳደርና ጸረ-ሙስናዳይሬክቶሬትተጠሪነቱ ለጽ/ቤቱ ኃላፊ ሆኖየሚከተሉትንተግባርናኃላፊነትይኖሩታል፡-

  • በሚኒስቴር መ/ቤቱ የሥነ ምግባር ደንቦች እና የፀረ ሙስና ሕጎች መከበራቸውን ይከታተላል፣ ስለ አፈፃፀማቸውም የመሥሪያ ቤቱን የበላይ ኃላፊ ያማክራል፤
  • በተቋሙ ሀብታቸውንና የገንዘብ ጥቅማቸውን እንዲያስመዘግቡ ሕግ የጣለባቸውን የመሥሪያ ቤቱን ሠራተኞች ሀብትና የገንዘብ ጥቅሞች መዝግቦ ለሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ለኮሚሽን ያስተላልፋል፤
  • ለሙስና ቀዳዳ የሚከፍቱ የአሠራር ዘዴዎችን ለማስተካከል /ለመድፈን/ የሚያስችሉ የአሰራር ዘዴዎችና ስልቶች እንዲጠኑ አማራጭ ሃሳቦችን ለመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ያቀርባል፣ ሲወሰንም ተግባራዊነቱን ይከታተላል፤
  • እንደ የመሥሪያ ቤቱ መርሃ ግብር /በሳምንት፣ በሁለት ሳምንት፣ በወር፣ በሩብ ዓመት፣ በመንፈቅ ዓመት/ በሚካሄዱ የእቅድ ግምገማዎች ወቅት በዳይሬክቶሬቶች ውስጥ በተከሰቱ የሥነ ምግባር ችግሮች ላይ ሠራተኛው ውይይት እንዲያደርግ ለመሥሪያ ቤቱ ኃላፊ ያሳስባል፣ ስለአተገባበሩም ክትትል ያደርጋል፤
  • በኢ-ሥነ ምግባራዊ ችግሮች ላይ የተወሰዱ እርምጃዎችን ይከታተላል፣ሪኮርድ ይይዛል፣ ከርምጃው በኋላ ያለውን ሁኔታ ይገመግማል፣ ሪፖርትም ለመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ያቀርባል፤
  • በተቋም የስነ ምግባር መርሆዎች ጉድለት የጥቆማ አሠራር ስርዓት ይዘረጋል የጥቆማ አቅራቢዎች ማንነት በሚስጥር ይይዛል፣ የጥቆማ መቀበያ ስርዓት እንዲዘረጋ ያገርጋል፤
  • አግባብ ያላቸው ሕጎችና የመንግሥት ሠራተኞች የሥነ ምግባር ደንብ በመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች ዘንድ ተገቢ ግንዛቤ አግኝተው በአግባቡ እንዲተገብሩ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ጋር ተባብሮ ይሰራል፤
  • የመልካም የአስተዳደር መርሆዎች እንዲከበሩና የአገልግሎት አሠጣጥ ለሕዝብ ጥያቄ ተገቢ ላሽ ለመስጠት በሚያስችል መልክ እንዲስተካከል የመሥሪያ ቤቱን የበላይ ኃላፊ ያማክራል፤
  • የመንግሥት ባለሥልጣናት ወይም ሠራተኞች ሥልጣናቸውን መከታ በማድረግ በመሥሪያ ቤቱ አገልግሎት ተጠቃሚ ሕብረተሰብ መካከል አድልዎ እንዳይፈፅሙ ይከታተላል፣ ተፈፅሞ ሲገኝ ለመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ሪፖርት ያደርጋል፤
  • በወርሃዊ ወይም ዓመታዊ መጽሔት ውስጥ መልካም ሥነምግባርን የሚያወድሱና የሙስና አስከፊነት የሚገልጹ መጣጥፎችና ጥናታዊ ጽሁፎች እንዲካተቱ ጥረት ያደርጋል፤
  • የሠራተኞች ቅጥሮች፣የደረጃ ዕድገቶች የኮንትራትና የግዥና ሽያጭ የጨረታ ውሎችና አፈፃፀማቸው ላይ የሥነምግባር ደንብ እንዳይጣስና የሙስና ወንጀል እንዳይፈፀም ይከታተላል፣ተፈጽሞ ሲያገኝም ለመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፈ ሪፖርት ያደረጋል፤
  • በየበጀት ዓመቱ ስለሚያከናውናቸው ተግባሮች ዕቅድ፣ መርሃግብርና በጀት አዘጋጅቶ ለመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ያቀርባል፣ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በወር፣በሩብ ዓመትና ዓመታዊ ያቀርባል፣
  • የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለውስጥና ለውጭ ተገልጋዩች የሚሰጠዉ አገልገሎት አዋጆችን፤ ደንቦችንና መመሪያዎችን የተከተሉና የመልካም አስተዳደር መርሆችን የተከተሉ መሆናቸዉን ይከታተላል፣ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፡፡

Please publish modules in offcanvas position.

We use cookies to improve your experience on our website. By browsing this website, you agree to our use of cookies.